Wednesday, September 25, 2013

መስከረም 12

በዚህች ቀን የመላዕክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል መታሰቢያ ነው፤ አባቶቻችን ሊቃውንት ባዘዙት መሰረት ሁሌም ወርሃዊ በዓሉን እናት ቤተክርስቲያን ከዋዜማው ጀምራ በማህሌት በሰዓታት በመዝሙር በኪዳን በቅዳሴ በቁርባን ታከብረዋለች፤ በተመሳሳይ እመቤታችን 21 እንዲሁም በዓለ ወልድ 29 ሁሌም በየወሩ ልክ እንደ ዓመታዊ ክብረ በዓላት በብዙ ምስጋና ተከብረው ነው የሚውሉት።በየወሩ እነዚህ 5 ዕለታት ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ ልዩ ስፈራ አላቸው። ቅዱስ ፋሲለደስ መስከረም 11 ቀን ሰማዕት እስከሚሆን ድረስ ቅዱስ ሚካኤል ከአጠገቡ ሳይለይ ያጽናናው ያረጋጋው ነበር፤ከሞተም በኃላ ነፍሱን ተቀብሎ አሳረጋት ዘለዓለማዊ ተድላ ደስታ የሚገኝባት ዳግም የማይሞትበት የህይወት አገር አስገባት። በረከቱ ይደርብን። የመስከረም ድርሳነ ሚካኤል

LIKE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment