Sunday, July 13, 2014

ሐምሌ 7 እንኳን አደረሳችሁ


በዚህች ቀን አጋዕዝተ ዓለም ስላሴ በአብርሃም ቤት ተገኝተው ቤቱን የባረኩበት የአንድነታቸውንና ሶስትነታቸው ሚስጢር የገለጹበት ታላቅ በዓል ነው። ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን ሐምሌ 7 ዕረፍቱ ለአባ ሊባኖስ
ሲኖዳ ማለት ተአምኒ ምለት ነው። ሀገሩ እስክንድርያ ነው። አባት እናቱ ሠንላል የሚባል ቦታ ይኖሩ ነበር። አንድ ቀን እናቱ ውሃ ልትቀዳ ስትሄድ አባ ክርስሳርዮስ ደቀመዛሙርቱን አስከትሎ ሲሄድ አገኛት ቡርክት አንቲ ወቡሩክ ፍሬ ከርስኪ ለቀደሙት ቅዱሳን ወንድማቸው ለኋለኞችም አባታቸው የሚሆን ቡሩክ ፍሬ በማኅፀንሽ አለና የተባረክሽ ነሽ ብሎ 3 ጊዜ ራሷን ሳማት። ደቀመዛሙርቱ አባታችን ሴት አነጋግሮ አያውቅም ነበር ዛሬ ምን ሆኗል? አሉ ይህን አውቆ የልጇን ክብር ነግሯቸዋል።
ያደገው ያባቱን በጎች ሲጠብቅ ነው። ሌሊት መንጋውን አሰማርቶ እሱ ከጉድጓድ ገብቶ ሲጸልይ ያድር ነበር። አንድ አረጋዊ ከጉድጓድ ገብቶ ሲጸልይ አሥሩ ጣቶቹ እንደ ፋና ሲያበሩ አይቶ አባት እናቱን እንዲህ ያለ ደግ የወለዳችሁ ምን ብጹዓን ናችሁ አላቸው። እንዲህማ ከሆነ የእግዚአብሔር እንጂ የኛ አይደለም ብለው ለመምህር ሰጡት ሲሰጡትም ናሁ ይሰመይ አርስመቅሪዶስ ለኩሉ ዓለም እነሆ የባሕታውያን ራስ ይባላል የሚል ድምጽ ከወደላይ ተሰምቷል። ከዚህ በኋላ እየተማረ እያገለገለ በጾም በጸሎት ተወስኖ በትኅርምት ኗሪ ቢሆን መልአኩ የኤልያን አስኬማ የዮሐንስን ቅናት ሲሰጠው መምህሩ በራዕይ አየ በማግስቱም የሰጠሁህን ለሲኖዳ አልብሰው አለው መዓረገ ምንኩስና ሰጥቶታል።
በ431 ዓ.ም ለአውግዞተ ንስጥሮስ በቁስጥንጥንያ በተደረገው ጉባዔ ቅዱስ ቄርሎስን ተከትሎ ተገኝቷል። ንስጥሮስን አውግዘው ሃይማኖት መልሰው ሲመለሱ መርከበኞች ሊቀ ጳጳሳቱ በተሳፈረበት መርከብ አትሳፈርም ብለው ከለከሉት ጌታ ብሩህ ደመና አዞለት በዚያ ተጭኖ ሲሄድ በመርከቡ አንጻር ሲደርስ የመርከቡ ጣሪያ እንደመስታወት ሆኖላቸው እሱና ሊቀጳጳሳቱ ተያይተው እጅ ተነሣስተዋል። እኒያም ክብሩን አይተው ደግ ሰው አስቀይመናል ብለው ተጸጽተዋል። በመጨረሻም በስሙ ጥርኝ ውኃ ለደኃ እስከመስጠት ድረስ በጎ የሠራውን እንደሚምርለት ጌታ ቃል ኪዳን ሠጥቶት ሕማም ድካም ሳይሰማው በተወለደ በ120 ዓመቱ ዐርፏል። የጻድቁ ምልጃና በረከት በሁላችን ላይ አድሮ ይኑር አሜን።

No comments:

Post a Comment