Thursday, July 3, 2014

ሰኔ 9

ሰኔ 9 በዚህች ቀን ከተራራማው ከአፍሬም አገር አርማቴም ከተባለ ቦታ የወጣው የሐና ልጅ ታላቁ ነብይ ሳሙኤል አረፈ። ይህ ነብይ በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ገልአርታ ውስጥ ታቦት እንዳለው ሊቀ ብርሃናት መርቆርዮስ አረጋ የቅዱሳን ታሪክ በሚለው መጽሐፋቸው ጠቅሰውታል። ነብዩ ሳሙኤል በብዙ እንባ በታላቅ ትዕግስት የተገኘ ነብይ ነው ሐና መካን ሆና ለረጅም ዘመን ታለቅስ ነበር ሰዎችም ይዘባበቱባት ነበር ይህች የበቅሎ ዘመድ ቢወልዷት እንጂ የማትወልድ በኃጢያቷ ብዛት እየው እግዚያብሔር ልጅ ነሳት፤ደግሞ እኮ አታፍርም ወደ ቤተ እግዚያብሔር ትሄዳለች ይሏት ነበር፤ ከእለታት በአንዱ ቀን እጇን ወደላይ አንስታ ከንፈሯን እያንቀሳቀሰች በለሆሳስ እያለቀሰች ስትጸልይ ተመልክቶ ካህኑ ዔሊ ሳይቀር አንቺ ሰካራም በሎ ዘለፋት 1ኛ ሳሙ 1፤14። እግዚያብሔር ግን ጸሎቷን ሰማት እንባዋን አበሰላት ከልጅ በላይ ልጅ ሰጣት እርሷም እንዲህ ብላ ግሩም ምስጋና አመሰገነች ይህንን የሐና ምስጋና ቤተክርስቲያን ዘወትር ትጠቀምበታለች መዝሙረ ዳዊት የጸሎት መጽሐፍ ካልዎት ይህንን ምስጋና እዚያ ላይ ያገኙታል፤ ልቤ በእግዚአብሔር ጸና ቀንዴ በእግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ አፌ በጠላቶቼ ላይ ተከፈተ በማዳንህ ደስ ብሎኛል። እንደ እግዚአብሔር ቅዱስ የለምና፥ እንደ አምላካችንም ጻድቅ የለምና ከአንተ በቀር ቅዱስ የለም። አትታበዩ፥ በኩራትም አትናገሩ እግዚአብሔር አዋቂ ነውና፥ እግዚአብሔርም ሥራውን የሚመዝን ነውና፥ ከአፋችሁ የኵራት ነገር አይውጣ። የኃያላንን ቀስት ሰብሮአል፥ ደካሞችንም በኃይል ታጥቀዋል። ጠግበው የነበሩ እንጀራ አጡ ተርበው የነበሩ ከራብ ዐርፈዋል መካኒቱ ሰባት ወልዳለችና፥ ብዙም የወለደችው ደክማለች። ኡፈየው እንዴት ያለ ጣፋጭ ምስጋና ነው፤1ኛ ሳሙ 2፤1። ነብዩ ሳሙኤል ሳኦልን ከአህያ ጠባቂነት ጠርቶ በእስራኤል ላይ ያነገሰ ነው ዳዊትን ደግሞ ከእረኝነት ጠርቶ ለእስራኤል ያነገሰ ነው፤ ሳኦልን በእስራኤል ዳዊትን ለእስራኤል “በ” እና “ለ” የእነዚህን ቃላት ልዩነት የሐሙስ ውዳሴ ማርያም አንድምታው ላይ በስፋት ተጽፏል፤ ነብዩ ሳሙኤል በ 98 ዓመቱ አረፈ እስራኤልም ሁሉ ተሰብስበው አለቀሱለት፥ በአርማቴምም በቤቱ ቀበሩት። 1ኛ ሳሙ 25፤1

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment