Thursday, July 3, 2014

ሰኔ 27

ሰኔ 27 በዚህች ቀን ታሪኩ በሐዋርያት ስራ ምዕራፍ 9፤10 ላይ የተጠቀሰው ሐዋርያው ሐናንያ አረፈ። ቀድሞ ሳኦል የተባለው ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሲያሳድድ ድንገት በደማስቆ ታላቅ ብርሃን ይመታዋል በምድር ይወድቃል ዓይኑም ይታወራል፤ “ሳውል ሳውል ስለምን ታሳድደኛለህ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል ይለዋል፤ ለ 3 ቀን 3 ሌሊት ዓይነስውር ሆኖ ይቆያል።ከዚያም የዛሬዋን ቀን መታሰቢያውን የምናደርግለት ሐዋርያው ሐናንያ እጁን ጭኖ ጸለየለት ዓይኑንም አበራለት ከዚያ በኃላ ነው ቅዱስ ጳውሎስ የቤተክርስቲየን ምርጥ እቃ የሆነው። ሐዋርያው ሐናንያ በደማስቆ ኤጲስቆጶስ አድርገው ሾሙት ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን ወደቀናች ሀይማኖት መለሳቸው፤የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው ከዚህ በኃላ አረመኔው ንጉስ ሉክያኖስ ይዞ ብዙ መከራ አደረሰበት፤ አስገረፈው፤ በእሳት አቃጠለው፤ በፍላጻ አስነደፈው፤ በመጨረሻም በዛሬዋ ቀን በድንጋይ አስወግሮ ገድሎታል። ዳግመኛ በዛሬዋ ቀን ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በሉቃስ ወንጌል 16፤20 ታሪኩን የተናገረለት ዓልአዛር አረፈ። እንዲህ ይላል “… አልዓዛርም የሚባል አንድ ድሀ በቍስል ተወርሶ በደጁ ተኝቶ ነበር፥ ከባለ ጠጋውም ማዕድ ከሚወድቀው ፍርፋሪ ሊጠግብ ይመኝ ነበር፤ ውሾች እንኳ መጥተው ቍስሎቹን ይልሱ ነበር። ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት ይላል የዚህ ጻድቅ እረፍቱ ዛሬ ነው፤ ይህም ሰኔ 27 የሚነበበው ስንክሳር ላይ ተጽፏል።ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም የአባቶቻችንን በረከት ያሳትፈን። 
LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment