Thursday, July 3, 2014

ሰኔ 24

ሰኔ 24 በዚህች ቀን ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አባ ሙሴ ጸሊም አረፈ፡፡ አስቀድሞ ሽፍታ ወንበዴ ዘማዊ ጣኦት አምላኪ ነበር፤ በኃላ እንደ አብርሃም አምላኬ ማን ነው ብሎ ተመራመረ፤ ወደ አስቄጥስ ገዳም ብትሄድ አምላክህ ማን እንደሆነ ይነግሩሃል የሚል ራዕይ አየ ተመለከተ፤ ተነስቶም ሄደ አባ ኤስድሮስን አገኛቸው፤አጽናንተው አረጋግተው ወደ አባ መቃርስ ወሰዱት አባ መቃርስም ንስሃውን ተቀብለው ቀኖና ሰጡት ኃላም አመነኮሱት የሽፍቶች አለቃ የነበረው የመነኮሳት አለቃ እስከመሆን ደረሰ፤ ሰይፉን ወርውሮ ከፍቅር ጋር ተወዳጀ፤ሌሊት እየተነሳ ለሁሉም መነኮሳት ውኃ ይቀዳላቸው ነበር ሉሉም ይታዘዛቸው ነበር ትንሹም ትልቁም ሙሴ ይህን አድርግሊኝ ይሉታል አርሱም ሁሉንም እሺ ይላል፤ ራሱን ዝቅ አደረገ ትሁትም ሆነ፤ በጸሎቱ ዝናብ ያዘንብ ነበር፤ እድሜው መጨረሻ አካባቢ ቡራኬ ሊቀበል ከመነኮሳት ጋር ሆኖ ወደ አባ መቃርስ ሄደ አርሳቸውም ልጆቼ ከናንተ መካከል በሰማእትነት የሚሞት አለ ብለው ትንቢት ተናገሩ ሙሴ ጸሊምም አባቴ ያ ሰው እኔ ነኝ ሰይፍ የሚያነሱ በሰይፍ ይጠፋሉ የሚል ቃል አለ ይህን ጊዜ በጉጉት ስጠባበቀው ነበር አላቸው፤ እንደተባለውም የበርበር ሰዎች ገዳሙን ሊያጠፉ መጡ መነኮሳቱ ሲሸሹ ሙሴ እዚያው ቀረ ሌሎች ሰባት መነኮሳት ከአባታችን ጋር እንሞታለን ብለው አብረውት ሆኑ የበርበር ሰዎች ደረሱ ሁሉንም በሰይፍ ገደሏቸው፤ ይህም ሰኔ 24 ቀን ነው፤ የአባታችን የሙሴ ጸሊም ስጋው በገዳመ አስቄጥስ በክብር ይገኛል፤ ግብጻውን ቤተክርስቲያን ሰርተውለት ታቦት ቀርጸውለት በደንብ ያከብሩታል ገድሉን ጽፈውለታል ፊልምም ሰርተውለታል ይህን ፊልም የኛ ሰዎች ግሩም አድርገው ወደ አማርኛ መልሰውታል፡ የቻለ ገድሉን ያንብብ ያልቻለም ፊልሙን ይመልከተው፤ የዛሬዋን ቀን ስለ ተክለሃይማኖት ብቻ በለን አንመጽውት ስለ ሙሴ ጸሊምም እያልን ይሁን፤ አምላከ ተከልዬ ጠብቀኝ ስንል አምላከ ሙሴ ጸሊም አትርሳኝ ማለትን አንርሳ ይህ ድንቅ አባት የማይረሳ ነውና፡፡ ሙሴ ጸሊም ማለት ሙሴ ጥቁር ሰው ማለት ነው፤ መልኩ ጥቁር ስለሆነ ነው ጥቁሩ ሙሴ ተብሎ የተጠራው፤ እገሌ ጥቁር ሰው እገሌ ጥቁር ስው አሁን የመጣ አይደለም፤ ኳስ መቶ ጎል ያገባ በሙሉ እገሌ ጥቁር ሰው መባል ጀምሯል፤ ቤተክርስቲን ግን ጥንቱንም ቢሆን አንዱን ቅዱስ ከአንዱ ለመለየት ቅጽል ስም ትሰጣለች ለምሳሌ ዮሐንስ አጺር አጭሩ ዮሐንስ ስምኦን ጫማ ሰፊው ሙሴ ጸሊም ጥቁሩ ሰው ሙሴ……ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን፡፡
LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment