Tuesday, November 5, 2013

ጥቅምት 25

ጥቅምት 25
በዚህች ቀን አቡነ አቢብ አረፈ፤ሮማዊ ነው፤ጻድቅ ወሰማእት ይለዋል እንደ ሰማእታት ተጋድሏል እንደ ጻድቃንም በገዳም ኖሯል፤ ወላጆቹ በህጻንነቱ ሞቱበት፤እድሜው አስር ዓመት ሲሆን ለጣኦት መስገድን የሚያዝ መኮንን መጣ፤ አቡነ አቢብም መኮንኑ ፊት ቆሞ ጣኦቶቹን ረገመበት፤የአካሉን ትንሽነት አይቶ መኮንኑ ተደነቀ ይላል፤ ግን ከማሰቃየት ወደ ኃላ አላለም በመንገድ እስጎተተው፤አስገረፈው፤ስጋውን ሰነጣጠቀው እጅና እግሩን በመጋዝ አስቆረጠው፤ልዩ ልዩ ጸዋትኦ መከራ አደረሰበት ሚያዚያ 18 ቀን አንገቱን በሰይፍ ቆርጦ ገደለው፤ ቅዱስ ሚካኤል ከሞት አስነሳው፤ወደ አንድ ገዳምም ወሰደው፤ መስቀልና አስኬማ ሰጥቶ በዚያው ገዳም እንዲጋደል አዘዘው፤ለ 42 ዓመት እህል ውሃ ሳይቀምስ በተጋድሎ ኖረ፤ የእረፍቱ ቀን ሲደርስ ጌታችን እልፍ አእላፍ መላእክትንና ቅዱሳንን አስከትሎ ተገለጸለት ፤ ስምህን የሚጠራ መታሰቢያህን የሚያደርገውን እኔ ኃጢያቱን ይቅር እለዋለሁ ብሎ ብዙ ቃል ኪዳን ገባላት፤ ማቴ 10፤41 በዛሬዋ ቀንም በመላእክት ዝማሬ ነፍሱ ከስጋው ተለይታለች፤ ከአቡነ አቢብና ከሰማእቱ መርቆርዮስ በረከት ያሳትፈን፤
LIKE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment