Monday, November 11, 2013

ህዳር 1

ህዳር
እነሆ የተባረከ የህዳር ወር ባተ፤ ይህ ወር ቀኑ 10 ሰዓት ነው ሌሊቱ 14 ሰዓት፤ ቀኑ አጭር ነው ቶሎ ይመሻል፤ ሌሊቱ ደግሞ ረጅም ነው ቶሎ አይነጋም፤ ይህንንም ለማረጋገጥ ማታ 12 ሰዓት ላይ ሰዓትን መመልከት ነው በጣም ይጨላልማል፤ ታህሳስ ላይ ከዚህም ይጨምራል ቀኑ 9 ሰዓት ሌሊቱ 15 ሰዓት ይሆናል፤ ለዚህም ነው የገና ጀምበር የሚባለው፤ ህዳር 1 በዚህች ቀን በከሃዲው ንጉስ በዳኬዎስ ዘመን አራቱ ቅዱሳን በሰማዕትነት አረፈፉ፤ የእነዚህም ስማቸው መክሲሞስ፤ፍሊጶስ፤ፊቅጦርና፤ማንፍዮስ ነው፤ ንጉሱ ላቆመው ምስል አንሰግድም ጌታ አንዱ እግዚያብሔር ብቻ ነው ብለው ጮኹ ይላል፤ ንጉሱ ይህን ሰምቶ ተቆጣ በጅራፍ ገረፋቸው፤ በጋለ የብረት በትር ደበደቸው፤በበርኖስ እላቂ ጨርቅ ቆምጣጣና ጨው ነክረው ቁስላቸውን አሿቸው ይህንን ሁሉ ታገሱ በመጨረሻ በሰይፍ ትንሽ ትንሽ አካላቸውን እየቆራረጡ ገደሏቸወው፤ እነርሱም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ፤ በጸሎታቸው የሚገኝ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።

LIKE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment