Sunday, November 24, 2013

ህዳር 15


ህዳር 15
መንፈቀ ህዳር የጾመ ስብከት መጀመሪያው ነው፤ ጾመ አዳም፤ ጾመ ነቢያትም ይለዋል የአዳም ተስፋ የነቢያት ትንቢት ተፈጽሞበታልና፤ ይህንን ጾም እመቤታችን ሰማይና ምድር የማይወስኑትን በሆዴ ተሸክሜ ምን ሰርቼ እወልደዋለሁ ስትል ጾማዋለች፤ሐዋርያትም ትንሳኤውን አብይ ጾምን ጾመን እናከብራለን ልደቱን ምን ሰርተን እናክብር ሲሉ ጾመውታል፤
ህዳር 15 በዚህች ቀን ቅዱስ ሚናስ አረፈ፤ ይህ አባት የአገር ገዢ ልጅ ነው፤ አባቱ በ 12 ዓመቱ ሞተ ከ 3 ዓመት በኃላ እናቱም አረፈች፤ ብቻውን ቀረ፤ መኳንንቱ አባቱን በጣም ይወዱት ነበርና በአባቱ ፋንታ ምስፍና ሾሙት፤ ግን ብዙም አልቆየም ዲዮቅልጥያኖስ “አብያተክርስቲያና...ት ይዘጉ አብያተ ጣኦታት ይከፈቱ በክርስቶስ የሚያምኑ በሰይፍ ይታረዱ” ሲል አዋጃ ነገረ፤ብዙዎች በሰማዕትነት ሞቱ ቀዱስ ሚናስ ግን ሹመቱን ትቶ ወደ ገዳም ገባ በተጋድሎም ኖረ ከእለታት በአንዱ ቀን ሰማይ ተከፍቶ ሰማዕታት የብርሃን አክሊል ሲቀዳጁ አየ፤አልዋለም አላደረም ወደ ከተማ ተመለሰ የክርስቶስ ባሪያ ነኝ ሲል ድምጹን አሰምቶ ተናገረ፤ አገሬው በጣም ይወደው ነበርና እንዳይሞትባቸው ፈርተው እባክህን ዝም በል አሉት፤ መኮንኑም ሊሸነግለው ሞከር ቅዱስ ሚናስ ግን እምቢኝ አለ ከዚህ በኃላ ልዩ ልዩ ጸዋትኦ መከራ አደረሱበት በመጨረሻም በዛሬዋም ቀን አንገቱን ቆርጠው ገደሉት የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ፤ ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከሰማዕቱ በረከት ያድለን።
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment