Thursday, January 30, 2014

ጥር 23

"ሌትና ቀን በልመናዬ ሳላቋርጥ ስለማስብህ እንደ አባቶቼ አድርጌ በንጹሕ ሕሊና የማመልከውን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፤ እንባህን እያሰብሁ በደስታ እሞላ ዘንድ ላይህ እናፍቃለሁ። በአንተ ያለውን ግብዝነት የሌለበትን እምነትህን አስባለሁና፤" 1ኛ ጢሞ 1፤ 1 ይህን መልዕክት ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀመዝሙሩ ቅዱስ ጢሞቲዎስ የላከለት ነው። ዛሬ ጥር 23 ቀን የዚህ የከበረ ሐዋርያ የጢሞቲዎስ የእረፍት ቀኑ ነው፤ አገሩ ልስጥራን ፤ አባቱ ኮከብ ቆጣሪ እናቱ አይሁዳዊት ነበሩ በኃላ በቅዱስ ጳውሎስ ስብከት አምነው ተጠምቀዋል ቅዱስ ጳውሎስ ጢሞቲዎስን ባየው ጊዜ ወደደው የእግዚያብሔር ጸጋ በላዩ ላይ ነበርና ይላል ሐዋ 16፤ 1 አስከትሎታል ብዙ አገርም አብሮት ዞሮ አስተምሯል ታላቅ መከራ ብዙ ሐዘን ደርሶበታል በኃላም ብቃቱን አይቶ በኤፌሶን ኤጲስ ቆጶስ አድርጎ ሾሞታል በዚያም ብዙዎችን ወደ ቀናች ኃይማኖት መልሷል በመጨረሻም በዛሬዋ ዕለት በሰማእትነት አርፏል። በረከቱ ይደርብን።


LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment