Tuesday, July 2, 2013

ሰኔ 25



በዛሬዋ ቀን ከሰባሁለቱ አርድእት አንዱ የሆነው የፀራቢው የዮሴፍ ልጅ ሐዋርያው ይሁዳ አረፈ፡፡ ይህ ሐዋርያ በመጽሐፍ ቅዱስ አንድ ምዕራፍ ብቻ ያለው የይሁዳ መልዕክትን የጻፈ ነው፤ በተለያዩ አገሮች በመዞር ህዝቡን ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚያብሔር መለሰ ብዙዎችንም ክርስቲያን አደረገ፤ በመጨረሻም ሐራፒ በሚባል አገር ገብቶ ሲያስተምር ጣኦት አምላኪዎች ይዘው አሰቃዩት፤ሰቀሉት በዛሬዋም ቀን በፍላጻ ነድፈው ገደሉት፤ቅድስት ነፍሱን ሰጠ፡፡ በረከቱ ይደርብን

No comments:

Post a Comment