Tuesday, February 18, 2014

የካቲት 5

የካቲት 5 በዚህች ቀን አስቀድሞ ኃጢያተኛ የነበረው አባ ዕብሎይ አረፈ። ይህ አባት ከኃጢያት ስራ ምንም የቀረው የለም ማመንዘር መስረቅ መግደል የዘወትር ተግባሩ ነበር፤ ከሁሉም የከፋው ግን ከዕለታት በአንዱ ቀን አንዲት ሴት የመውለጃዋ ቀን ደርሶ ስታምጥ አየ ሰይጣን በልቡ ክፉ ሐሳብ ጨመረበት ህጻኑ እንዴት እንደተኛ ለመመልከት የሴቲቱን ጸጉር ይዞ ከምድር ጣላት በሾተልም ሆዷን ቀደደው ተሰቃይታ በፃር ሞተች ህፃኑም አልቆየም እናቱን ተከተላት፤ ከዚህ በኃላ የሰራውን ስራ አስቦ ደነገጠ አዘነ መራራ ለቅሶም አለቀሰ በትሩን ብቻ ይዞ ወደ በርሃ ሮጠ እራሱን የሚያስጠጋበት ዋሻ አልፈለገም ከአራዊት ጋር የሚኖር ሆ...ነ እንጂ ቅጠል እየበላ የቀን ሐሩር የሌሊት ቁር እየተፈራረቀበት 40 ዓመት እያለቀሰ ጽኑ ገድል ተጋደለ ሰውነቱ ጥላሸት መሰለ ቆዳው ከአጥንቱ ተጣበቀ፤ የጌታ ቃል መጣለት እንዲህ የሚል "ስለሴቲቱ ደም እግዚያብሔር ይቅር ብሎሃል ጽና በርታም" አለው የበለጠ የሚጋደል ሆነ ከአንድ ዓመት በኃላ 70 ዓመት ሙሉ የሰው ፊት ሳያይ ዘግቶ የኖረ ባህታዊ ወደርሱ ላከለት የሆነውን ነገር ሁሉ ነገረው አይዞህ እግዚያብሔር ይቅር ብሎሃል ነገ የጌታ መልአክ የክርስቶስን ስጋና ደም ሊያቀብልህ ይመጣል ተዘጋጅ አለው፤ እንዳለውም እሁድ ሰንበት ጠዋት የጌታ መልአክ በመነኩሴ አምሳል ስጋ ወደሙን ይዞ ተገለጸ ከዚያ ቀድም እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ነፍስን የሚያለመልም ጣፋጭ መዓዛ ሸተተው ስጋ ወደሙን ተቀበለ ጠቁሮ የነበረ ሰውነቱ ጸአዳ መሰለ እንደ ፀሐይም አበራ በበነጋው የካቲት 5 መልአክት ነፍሱን ተሸክመው እየዘመሩ ወደ አርያም በረሩ፤ ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን። ከዚህ በኃላ መልአኩ ለዚያ ባህታዊ "ሰው ከእግዚያብሔር ምህረት ተስፋ እንዳይቆርጥ በኃጢያት ለወደቁ አለኝታ ይሆን ዘንድ የአባ ዕብሎይን ገድሉን ጽፈሕ ለመነኮሳቱ ስጣቸው" አለው፤ እንደተባለውም አደረገ። እየው እኛም ሰማነው አነበብነው መሐሪነትህን እንናገራለን ይቅርባይነትህንም እንመሰክራለን፤ እንዲህ እያልን "ስለዚህ ልቤን ደስ አለው ምላሴም ሐሴት አደረገች፤ ሥጋዬም ደግሞ በተስፋ ታድራለች፤ ነፍሴን በሲኦል አትተዋትምና" መዝ 16፤9 ከጻድቁ በረከት ያሳትፈን፡፡

LIKE OUR PAGE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment