Tuesday, February 25, 2014

የካቲት 15

በዚህች ቀን የበራክዩ ልጅ ነብዩ ዘካርያስ አረፈ፤ ቁጥሩ ከደቂቀ ነብያት ነው፤ ብዙ ትንቢቶችን ተናግሯል ስለ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ስቅለት ዘካ 1210 የወጉትን ያዩታል አለ፤ ዳግመኛም ስለ ሆሳህና እንዲህ አለ "ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል፤" ዘካ 99 ስለደብረዘይት ዳግም ምጽአትም ተናግሯል ዘካ 145 ይሁዳ ክርስቶስን 30 ብር እንደሚሸጠው ዘካ 1112 ይህ ነብይ ደግሞ ስለ ጾም እንዲህ ሲል ተናግሯል "የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። የአራ...ተኛው ወር ጾም የአምስተኛውም የሰባተኛውም የአሥረኛውም ወር ጾም ለይሁዳ ቤት ደስታና ተድላ የሐሤትም በዓላት ይሆናል፤ ስለዚህም እውነትንና ሰላምን ውደዱ።" ዘካ 819 ሌሎች ብዙ ትንቢቶችን ተናገረ፤ ትንቢት የሚናገርበት ወራት ሲፈጸም የካቲት 15 በዛሬዋ ቀን አንቀላፋ በአባቶቹ ነብያት መቃብርም ቀበሩት። በረከቱ ይደርብን።
"በአሕዛብም መካከል ብዘራቸው እንኳ በሩቅ አገር ሳሉ ያስቡኛል፥ ከልጆቻቸውም ጋር በሕይወት ይኖራሉ፥ ይመለሱማል።" ዘካ 109 አሜን በስደት ያሉ ኢትዮጰያውያን ወገኖቻችንን ይመልስልን።

No comments:

Post a Comment