Monday, June 9, 2014

ግንቦት 26

ግንቦት 26 
በዚህች ዕለት ዲዲሞስ የተባለው ሐዋርያው ቶማሰ አረፈ፤ እርሱም በላይንደኬ በዛሬዋ ህንድ ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን አሳመነ በዚህም መኮንኑ ተቆጥቶ ጽኑ ስቃይ አሰቃየው ቆዳውንም ገፈፈው፤በሰውነቱም ላይ ጨውና ቆምጣጣ አፈሰሱበት፤ይህንን ሁሉ ታገሰ፤በተገፈፈ ቆዳው ስምንት ሙታን አስነሳ ብዙ ገቢረ ታአምራትን አደረገ፤ይህንን አይተው መኮንኑን ጨምሮ ብዙዎች አመኑ።ከዚህ በኃላ በአቴናና መቄዶንያ ገብቶ ሰበከ ንጉሱም ይዞ አሰቃየው በመጨረሻም በጦር ተወግቶ በዛሬዋ ዕለት በሰማዕትነት አረፈ። የጌታን ጎን የዳሰሰች የሐዋርያው ቀኝ እጅ ተአምራትን እያደረገች እስከ ዛሬ በህንድ አለች፤
በረከቱ ይደርብን

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment