Thursday, October 31, 2013

ጥቅምት 4

ጥቅምት 4
በዚህች ቀን የኢትዮጵያ ባለውለታዎች፤ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ እንድትሆን ትልቁን ድርሻ ያበረከቱ አብርሃና አፅብሃ የእረፍት ቀናቸው ነው፤እነዚህ ሁለት ጻድቅ ነገስታት ወንድማማች ሲሆኑ የክርስትና እምነትን በኢትዮጽያ ያበሩ አማናዊ ጥምቀትንና ቁርባን ያስጀመሩ ከመሆናቸው ባሻገር ከ 154 በላይ አብያተክርቲያናት አንጸዋል፤ ከነዚህም በተለይ ዋንኞቹ ትግራይ ውስጥ ገልአርታ ቀመር አርብአቱ እንስሳ፤ጋሞ ጎፋ ብርብር ማርያም፤ጎጃም መርጡለማርያምና ዲማ ጊዮርጊስ፤ የብሐ ጊዮርጊስ ከፋ፤የዋሻ ሚካኤል ሰላሌ፤ የጀንባ ሚካኤል ሰማዳ፤ እንዲሁም በአዲስ አበባ የካ ሚካኤልንና የረር በዓታ ተጠቃሽ ናቸው። ከሁሉም በላይ ዓለም ዛሬም ድረስ የሚገረምባቸውን የአክሱም ሀውልቶች ያቆሙ ናቸው፤ 33 ሜትር ተኩል ድንጋይን ከየት አመጡት እንዴትስ ቀረጹት እንዴትስ ብለው አቆሙት ይህ የእግዚያብሔር ተአምር ነው እንጂ፤ እኛስ እጹብ ግሩም ብቻ ብለን እናልፋለን። በኢትዮ ከነገሱ ከጥንት ነገስታት እንደ አብርሃና አጽብሃ በርካታ ታሪክን አኑሮልን ያለፈ ንጉስ የለም ብንል አልተሳሳትንም፤ እነዚህ ቅዱሳን የኢትዮጵያን ድንበር አስፍተው ክርስትናን አጽንተው ያስረከቡን ዋኖቻችን ናቸው፤ሁለቱም በተለያየ ዓመተ ምህረት ጥር 4 ቀን አርፈዋል፤ኢትዮጰያ ውስጥ በስማቸው ሰባት ቤተክርስቲያን እንዳላቸው ሊቀ ብርሃናት መርቆሪዎስ አረጋ የቅዱሳን ታሪክ በሚለው መጽሀፋቸው ጠቅሰውታል፤ ጥር 4 ቀን በተለይ በሰሜኑ ኢትዮጵያ በደማቁ ተከብረው ይውላሉ። በረከታቸው ይደርብን። 

No comments:

Post a Comment