Monday, January 10, 2022

የእመቤታችን ሥዕል ከመንበር ላይ ለምን ይቀመጣል?

 ይህን ያውቁ ኖሯል?

የእመቤታችን ሥዕል ከመንበር ላይ ለምን ይቀመጣል?
በኦሪቱ የኪሩቤል ሥዕል በታቦቱ አጠገብ ይቀመጥ ነበር፡፡ ዘጸ. ፳፭፥፳፩-፳፪፤ዘኊ ፯፥፹፱፡፡ እግዚአብሔር ለሙሴ ነግሮ እንዲህ እንዲሆን ያደረገበት ምክንያት አለው፡፡ይህም ምክንያት ኪሩቤል የመንበሩ /የዙፋኑ/ ተሸካሚዎች በመሆናቸው ነው፡፡ ፩ኛ ሳሙ.፬፥፬፤ ሕዝ.፩፥፭፰፤ ፲፥፲፪፤ ፳፩፤ራእ.፬፥፮፡፡ በአዲስ ኪዳን ደግሞ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአዲስ ኪዳን ኪሩብ ትባላለች፡፡ እንዲያውም ከኪሩቤል ትበልጣለች፡፡ ኪሩቤል የሚሸከሙት መንበሩን ነው፤ እመቤታችን ግን ማኅፀኗን መንበር አድርጋ እርሱን ተሸከመችው፡፡ እንግዲህ በብሉይ ኪዳን ዘመን በእግዚአብሔር ትእዛዝ የኪሩቤል ሥዕል በመንበረ ታቦቱ ይቀመጥ እንደ ነበር በአዲስ ኪዳን ደግሞ ኪሩብ የምትባል እመቤታችን ሥዕሏ በመንበረ ታቦቱ ላይ ይቀመጣል፡፡
ምንጭ፡ ነገረ ቅዱሳን ቁ. ፩




No comments:

Post a Comment