Friday, April 11, 2014

መጋቢት 22

መጋቢት 22 ጥንተ ሆሳዕና ፤ ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በአህያና በአህያይቱ ውርንጫ ተቀምጦ ወደ እየሩሳሌም የገባበት ከሁለት ሺ ዓመት ገደማ በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ነው። ጥንተ ሆሳዕና የሚባለውም ለዚያ ነው፤ ነገር ግን በዲሜጥሮስ ቀመር መሰረት ሆሳዕና እሁድን ሳይለቅ ከትንሳኤ አንድ ሳምንት ቀድሞ እንዲከበር ቤተክርስቲያን ስርዓት ብትሰራም ቅሉ መጋቢት 22 ይህንን ቀን ''ጥንተ ሆሳዕና" ብላ አስባው ትውላለች። በዛሬው ቀን የሚነበቡት ምንባባት በሙሉ ሆሳዕናን የሚመለከቱ ናቸው፤ ቅዳሴውም ቅዳሴ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ነው፤ ምክንያቱም በዚህ ቅዳሴ ውስጥ ስለ ሆሳዕና በስፋት ይናገራልና፤ ምስባኩም መዝ 8፤2 " ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ" የሚነበበው ወንጌልም ከአራቱ ወንጌላውያን የአንዱ ሆሳዕናን የሚመለከተ ነው፤ ማቴ 21፤4። ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን።

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment