Friday, April 11, 2014

ኒቆዲሞስ



የዐቢይ ጾም ሰባተኛው ሰንበትና ሳምንቱ ኒቆዲሞስ ይባላል። ኒቆዲሞስ የተባለበትም ምክንያት በዚሁ ሰንበት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ «ወሀሎ አሐዱ ብእሲ እምፈሪሳውያን ዘስሙ ኒቆዲሞስ መልአኮሙ ለአይሁድ ዞሖረ ኃቤሁ ቀዲሙ ሌሊተ ወይቤሎ ለኢየሱስ ዕጓለ አንበሳ ሰከብከ ወኖምከ አንሥአኒ በትንሣኤከ፡- ስሙ ኒቆዲሞስ የሚባል የአይሁድ አለቃ የሆነ ከፈሪሳውያን ወገን አንድ ሰው ነበረ፡፡ እሱ አስቀድሞ ሌሊት ሄዶ ኢየሱስን በመቃብር አንቀላፋህ በትንሣኤህ አንሣኝ» ያለው ነው፡፡
ኒቆዲሞስ ሰገደ መንፈቀ ሌሊት ለዘቀደሳ ለሰንበት፡- ሰንበትን ለአከበራት ጌታ ኒቆዲሞስ ኢየሱስን ረቢ አብ መምህር ሆነህ ከአብ ዘንድእንደመጣህ እናምንብሃለን አለው፡፡» እያለ ኒቆዲሞስ ሌሊት ወደ ጌታችን ኢየሱስ እየሔደ ይሰግድ እንደነበረና ምሥጢረ ጥምቀትን ከእሱእንደተማረ እየጠቃቀሰ እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህ ሰንበት ለዚሁ ጌታችን ኢየሱ
ስ ክርስቶስ ኒቆዲሞስ ከጌታ ለመማሩ መታሰቢያ ሆኖ ስለተሰጠነው፡ የዚህ በዓል ታሪክ ዝርዝር ሁኔታው በዮሐንስ ወንጌል ምዕ 3 ቁጥ 1 እስከ 21 ተጽፏል፡፡
በዚህ ክፍለ ወንጌል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ ምሥጢረ ጥምቀትን ብቻ ሳይሆን ርደቱን፣ ስቅለቱን፣ አዳኝነቱን አስተምሮታል፡፡ኒቆዲሞስ ከአርማትያሱ ከዮሴፍ ጋር ሆኖ ጌታን የገነዘው ታላቅ ሰው ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ሰንበት ከዚህ ጀምሮ የኒቆዲሞስ መታሰቢያ እስከ 3 ቀንይከበራል ማለት ማክሰኞ ድረስ የኒቆዲሞስ ቀኖች ናቸው፡፡
ሮሜ 7፡1-19
«ወንድሞች ሆይ ሕግን ለሚያውቁ እናገራለሁና ሰው ባለበት ዘመን ሁሉ ሕግ እንዲገዛው አታውቁምን) ያገባች ሴት ባልዋ በሕይወት ሲኖርከእርሱ ጋር በሕግ ታስራለችና፤ ባልዋ ቢሞት ግን ስለ ባል ከሆነው ሕግ ተፈትታለች፡፡ ስለዚህ ባልዋ በሕይወት ሳለ ለሌላ ወንድ ብትሆንአመንዝራ ትባላለች፤ ባልዋ ቢሞት ግን ከሕጉ አርነት ወጥታለችና ለሌላ ወንድ ብትሆን አመንዝራ አይደለችም፡፡
እንዲሁ ወንድሞቼ ሆይ እናንተ ደግሞ በክርስቶስ ሥጋ ለሕግ ተገድላችኋል ለእግዚአብሔር ፍሬ እንድናፈራ እናንተ ለሌላው ከሙታን ለተነሣውለእርሱ ትሆኑ ዘንድ፡፡ በሥጋ ሳለን በሕግ የሚሆን የኃጢአት መሻት ለሞት ፍሬ ሊያፈራ በብልቶቻችን ይሠራ ነበርና፤ አሁን ግን ለእርሱለታሰርንበት ስለ ሞትን ከሕግ ተፈትተናል ስለዚህም በአዲሱ በመንፈስ ኑሮ እንገዛለን እንጂ በአሮጌው በፊደል ኑሮ አይደለም፡፡
እንግዲህ ምን እንላለን) ሕግ ኃጢአት ነውን) አይደለም፤ ነገር ግን በሕግ ባይሆን ኃጢአትን ባላወቅሁም ነበር፤ ሕጉ አትመኝ ባላለ ምኞትንባላወቅሁም ነበርና፡፡ ኃጢአት ግን ምክንያት አግኝቶ ምኞትን ሁሉ በትእዛዝ ሠራብኝ፤ ኃጢአት ያለ ሕግ ምውት ነውና፡፡ እኔም ዱሮ ያለሕግሕያው ነበርሁ፤ ትእዛዝ በመጣች ጊዜ ግን ኃጢአት ሕያው ሆነ እኔም ሞትሁ፤ ለሕይወትም የተሰጠችውን ትእዛዝ እርስዋን ለሞት ሆና አገኘኋት፤ኃጢአት ምክንያት አግኝቶ በትእዛዝ አታሎኛልና በእርስዋም ገድሎኛል፡፡ ስለዚህ ሕጉ ቅዱስ ነው ትእዛዚቱም ቅድስትና ጻድቅት በጎም ናት፡፡
እንግዲህ በጎ የሆነው ነገር ለእኔ ሞት ሆነብኝን) አይደለም ነገር ግን ኃጢአት ሆነ፤ ኃጢአትም በትእዛዝ ምክንያት ያለልክ ኃጢአተኛ ይሆን ዘንድኃጢአትም እንዲሆን ይገለጥ ዘንድ በጎ በሆነው ነገር ለእኔ ሞትን ይሠራ ነበር፡፡ ሕግ መንፈሳዊ እንደሆነ እናውቃለንና፤ እኔ ግን ከኃጢአት በታችልሆን የተሸጥሁ የሥጋ ነኝ፡፡ የማደርገውን አላውቅምና፤ የምጠላውን ያን የማደርገው አሁን እኔ አይደለሁም በእኔ የሚያድር ኃጢአት ነው፡፡እንጂ፡፡ በእኔ ማለት በሥጋዬ በጎ ነገር እንዳይኖር አውቃለሁና፤ ፈቃድ አለኝና መልካሙን ግን ማድረግ የለኝም የማልወደውን ክፉውን ነገርአደርጋለሁና ዳሩ ግን የምወደውን በጎውን ነገር አላደርገውም፡፡»
1 ዮሐ 4፡18
«ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም፡፡ እርሱአስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን፡፡ ማንም እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል) እግዚአብሔርንም የሚወድ ወንድሙን ደግሞ እንዲወድ ይህች ትእዛዝ ከእርሱ አለችን፡፡»
፡ሥራየሐዋ
«ነገር ግን በሕዝቡ ሁሉ ዘንድ የከበረ የሕግ መምህር ገማልያል የሚሉት አንድ ፈሪሳዊ በሸንጎ ተነሥቶ ሐዋርያትን ጥቂት ፈቀቅ እንዲያደርጉአቸውአዘዘ፡፡ እንዲህም አላቸው የእሥራኤል ሰዎች ሆይ ስለ እነዚህ ሰዎች ምን እንደምታደርጉ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፡፡ ከዚህ ወራት አስቀድሞ ቴዎዳስእኔ ታላቅ ነኝ ብሎ ተነሥቶ ነበርና አራት መቶ የሚያህሉ ሰዎችም ከእርሱ ጋር ተባበሩ፤ እርሱም ጠፋ የሰሙትም ሁሉ ተበተኑ እንደ ምናምንምሆኑ፡፡ ከዚህ በኋላ ሰዎች በተጻፉበት ዘመን የገሊላው ይሁዳ ተነሣ ብዙ ሰዎችንም አሸፍቶ አስከተለ፤ ከእግዚአብሔር እንደሆነ ግን ታጠፉአቸውዘንድ አይቻላችሁም፤ በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ፡፡
ሰሙትም ሐዋርያትንም ወደ እነርሱ ጠርተው ገረፉአቸው፤ በኢየሱስም ስም እንዳይናገሩ አዝዘው ፈቱአቸው፡፡ እነርሱም ስለስሙ ይናቁ ዘንድየተገባቸው ሆነው ስለ ተቈጠሩ ከሸንጎው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ፤ ዕለት ዕለትም በመቅደስና በቤታቸው ስለ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነማስተማርንና መስበክን አይተውም ነበር፡፡ »
፡መዝ
ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ
አመከርከኒ ወኢተረክበ ዓመጻ በላዕሌየ
ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው
ልቤን ፈተንኸው በሌሊትም ጐበኘኸኝ፡፡
ፈተንኸኝ ምንም አላገኘህብኝም፡፡
የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው፡፡
፡ዮሐ
«ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ መምህር ሆይእግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔርዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን አለው፡፡ ኢየሱስም መልሶ እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥትሊያይ አይችልም አለው፡፡ ኒቆዲሞስም፡- ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል) ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንደይችላልን) አለው፡፡ ኢየሱስም መለሰ እንዲህ ሲል፡- እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔርመንግሥት ሊገባ እይችልም፡፡ ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው፡፡ ዳግመኛ ልትወለዱ ያስፈልጋችኋል ስላልሁህአታድንቅ፡፡ ነፋስ ወደሚወደው ይነፍሳል ድምፁንም ትሰማለህ ነገር ግን ከወዴት እንደመጣ ወዴትም እንዲሄድ አታውቅም ከመንፈስ የተወለደሁሉ እንዲሁ ነው፡፡ ኒቆዲሞስም መልሶ ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል) አለው፡፡ ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፡- አንተ የእሥራኤል መምህርስትሆን ይህን አታውቅምን) እውነት እውነት እልሃለሁ የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውንም እንመሰክራለን ምስክራችንንም አትቀበሉትም፡፡ስለምድራዊ ነገር በነገርኋችሁ ጊዜ ካላመናችሁ ስለሰማያዊ ነገር ብነግራችሁ እንዴት ታምናላችሁ)»

ጐሥዓ ዘ እግዝእትነ ቅዳሴ

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment