Thursday, March 27, 2014

መጋቢት 14

በዚህች ቀን ከፍጹማን መነኮሳት አንዱ የሆነው አባ ባጥል አረፈ። ይህ አባት ከሌሎች አባቶች ለየት የሚያደርግው ቅድስና አለው፤ ታሪኩ እንዲህ ነው፤ በእስክንድርያ ያሉትን ሴተኛ አዳሪዎችን ስማቸውን መዘገበ ከዚያም ሰርቶ ለፍቶ የሚያገኛትን ጥሪት ለዕለት ጉርሱ የምትሆን የሽንብራ ቂጣ ይገዛበታል፤ የተረፈውን ገንዘብ ግን ሴተኛ አዳሪዎቹ ጋር ሄዶ ዛሬ ካንቺ ጋር ነው የማድረው ይልና ገንዘብ ሰጥቶ ይገባል ሌሊቱን ሙሉ ሲሰግድ ሲጸልይ ያድርና ጠዋት ይህንን ስራዬን ለማንም እንዳትናገሪ ብሏት አምሏት ይወጣል፤ በሚቀጥለው ቀን ደግሞ ሌላዋ ጋር ይገባል እንዲሁ ያደርጋል፤ ከዕለታት በአንዱ ቀን ግን አንዲ...ቷ ሴተኛ አዳሪ ማሃላዋን አፍርሳ ለሰዎች ተናገረች፤ " እርሱ ንጹህ መነኩሴ ነው ምንም ኃጢያት የለበትም እኛ እንዳናመነዝር ከኃጢያት ይጠብቀናል ሌሊቱን ሁሉ ሲሰግድ አድሮ ገንዘባችንን ከፍሎን ይሄዳል" ብላ ለሰዎች ተናገረች። ማሃላዋን ስላፈረሰች ጋኔን ይዞ አሳበዳት፤ ሌሎቹ እውነቷን ነው ብለው ለመመስከር ፈሩ ይላል። የዚህን አባት ስራውን ትህትናውን ፍቅሩን የተመለከቱ ሴተኛ አዳሪዎች ገሚሱ መንኩሰው ገዳም የገቡ አሉ፤ ገሚሶቹ ባል አግብተው የኖሩ አሉ፤ ጨርሰው ይህን ክፉ ስራ የተውም አሉ። የዛኑ ያህል ደግሞ ብዙ ሰዎች ባለማወቅ ይነቅፉት፤ ይሰድቡት፤ ይጸየፉትም ነበር፤ እርሱ ግን በትህትና ተጋድሎውን አበዛ መጋቢት 14 በዛሬዋ ቀን እንደተለመደው ሌሊቱን ሁሉ ሲሰግድ አድሮ ሊነጋጋ ሲል አረፈ የቤቱ ወለል ላይ " እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ" ማቴ 7፤1 የሚል ፅሑፍ ተጽፎ ተገኘ፤ ታሪኩም ለሁሉ ተገለጸ ብዙዎች ተገረሙ ዳን 5፤5። በጸሎቱ የሚገኝ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን። 

LIKE OUR PAGE >>>

No comments:

Post a Comment