Saturday, August 31, 2013

ነሐሴ 25



በዚህች ቀን እንድርያኖስ በሰማዕትነት አረፈ፤ ይህ ሰማዕት ቀድሞ የጣኦት አምላኪው ንጉስ የመክስምያኖስ መኮንን ነበር፤ 24 ቅዱሳን መክስምያኖስ ላቆመው ምስል አንሰግድም ብለው መከራ ሲቀበሉ ተመለከተ የልባቸውንም ጽናት አደነቀ፡፡ ይህንን ሁሉ መከራ የምትቀበሉት ምን እናገኛለን ብላችሁ ነው ሲልም ጠየቃቸው፤ እነርሱም ስለሚጠብቃቸው ተስፋ ስለክርስቶስ ሁሉንም ነገር ነገሩት፤ በዚህም የእንድርያኖስ ልቡ ተሰበረ፤ ወደ ንጉሱም ሄዶ በክርስቶስ ማመኑን ተናገረ፤ ንጉሱም አብደክ መሆን አለበት አለው፤ አንድርያኖስም የለም ቀድሞ ነበር ያበድኩት አሁን ግን ከእብደቴ ተመልሻለው አለው፡፡ ከዚህ በኃላ እስረት ቤት ወረወረው፤ የሆድ እቃው እስኪዘረገፍ አስደበደበው፤ በድጅኖ ጭኑን አስቀጠቀጠው ልዩ ልዩ መከራ አደረሰበት በመጨረሻም በዛሬዋ ቀን በሰማእትነት አረፈ፡፡ በረከቱ ይደርብን፡፡
LIKE >>>
https://www.facebook.com/pages/ተዋህዶ-ሀይማኖታችን/117298008428339?ref=hl

No comments:

Post a Comment