Tuesday, January 22, 2013

ጥር 15


 

ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት 4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ቀኑ ጥር 15 ሐሙስ ከሌሊቱ 6 ሰዓት የሶስት ዓመቱ ህጻን ቅዱስ ቂርቆስ በሰይፍ አንገቱ ተቆርጦ በሰማዕትነት አረፈ በበነጋው ዓርብ ጥር 16 ቀን እናቱ እየሉጣም በተመሳሳይ በሰማዕትነት አረፈች። እነዚህ ሰማዕታት ከመሞታቸው በፊት ብዙ መከራ ተቀብለዋል ከአገር አገር ተሰደዋል፤ ከተቀበሉት  መከራዎች የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ፈጠኖ ደራሽነቱን አማላጅነቱን ያየንበት ሐምሌ 19 ከእሳት ያዳነበት ቀን አንዱ ነው። በአገራችን ኢትዮጰያ በሰማዕቱ ቂርቆስ ስም በርካታ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት አሉ ከነዚህም የጣና ቂርቆስ ገዳም ዋንኛው ነው፤ በዚህ ገዳም ታቦተ ጽዮን ለረጅም ዘመን አርፋበታለች፤ የኦሪት መስዋትም ይሰዋበት ነበር፤ በአዲስ አበባ ለገሃር ባቡር ጣቢያ አካባቢ የሚገኘውን ቤተክርስቲያን የተከሉት ደገኛው ንጉስ እምዬ ምኒሊክ ናቸው የተከሉበት ምክንያትም  አዲስ አበባ ተስቦ በሽታ ገብቶ ህዝቡን እየጨረሰ ነበር፤ ታዲያ ምን ይሻላል ብለው ሽማግሌዎችን ሲያማክሩ፤ ጃንሆይገድለ ቂርቆስ ላይ እንዲህ የሚል ቃል ኪዳን አለ ቤተክርስቲያንህ ባለበት ቦታ ርሃብ ቸነፈር ፈጽሞ አይደርስም ይላል የሰማዕቱን ታቦት ቢያስመጡ ቤቱንም ቢሰሩለት ይህ ሁሉ መከራ ይወገዳል አሏቸው፤ የሽማግሌዎቹን ምክር ሰምተው አሁን ያለውን ቤተክርስቲያኑን አነጹ ታቦቱንም አስገቡ በዚህም በሽታው ወረርሺኙ ቀንሶላቸዋል ይላል፤በዚህ ቤተክርስቲያን ዛሬ ታቦተ ህጉ ወጥቶ በደማቁ ተከብሮ ይውላል። ከቅዱስ ቂርቆስ ከእናቱ እየሉጣም በረከታቸውን ያድለን።

No comments:

Post a Comment