Thursday, May 16, 2013

ግንቦት 9



በዚህች ቀን የጌታችን የመድሐኒታችንን የእየሱስ ክርስቶስን መስቀል ያገኘችው እሌኒ ቅድስት አረፈች። ይህችም የታላቁ ንጉስ የቆስጠንጢኖስ እናት ነች። ባለቤቷ ተርቢኖስ ይባላል ነጋዴ ነው ባህር ተሻግረው አገር አቋርጠው ለዓመት ሁለት ዓመት ነግደው ይመለሳሉ ከዕለታት በአንዱ ቀን ወደ አገገራቸው ሲመለሱ መርከብ ላይ ጨዋታ ጀመሩ፤ እኛስ በሠላም ወደ አገራችን ገባን ሚስቶቻችን ግን እንዴት ሆነው ይሆን አሉ ተርቢኖስ ሚስቱን እጅግ ያምናት ነበርና የእኔ ሚስት እንደዚህ ዓይነት ነገር አታውቅም የእናንተ ሚስቶች ያደርጉት ይሆናል እንጂ አላቸው፤ ያንተ ሚስት ከሄዋን ልጆች የተለየች ነችን እኔ ሄጄ ወድጃት ወዳኝ ...ለምጃት ለምዳኝ አፍቅሬት አፍቅራኝ ብመጣ ምን ትቀጣለህ አለው፤ እስከዛሬ የደከምኩበት ወረት ላንተ ይሁን ካልሆነልህ ግን ያንተን እወስዳለሁ አለው፤ በዚህ ተወራርደው ተለያዩ ቤቷ ሄደ አላስገባም አለችው፤ ገረዷን አስጠርቶ ሁለቱ ብቻ የሚተዋወቁበትን እቃ ስጪኝ ወርቅ ብር እሰጥሻለሁ አላት፤ እሺ አንተ ነጋዴዎች መጡ የብስ እረገጡ እያልክ በከተማው ለፍፍ አለችው እንዳለችው በከተማው እየዞረ ለፈፈ፤ ወደ እሌኒ ቅድስት ገብታ እመቤቴ ነጋዴዎች መጡ የብስ እረገጡ እየተባለ ነው ገላሽን ታጠቢ ሽቶም ተቀቢ አለቻት እርሷም ገላዋን ልትታጠብ የአንገት ሐብሏን አስቀምጣ ባኞ ገባች፤ የአንገት ሐብሏ የተርቢኖስ ስም አለበት ወስዳ ሰጠችው፤ እርሱም ሄዶ ‘’እየው ለምጃት ለምዳኝ ወድጃት ወዳኝ መጣሁ ውድ ስጦታም ሰጠችኝብሎ ሐብሉን አሳየው አልተጠራጠረም አመነው የለፋበትን ወረት በሙሉ አስረክቦ እያዘነ ወደ ቤቱ ገባ፤ ምነው ጌታዬ አዝነህ አይሃለሁ ምን ሆንክብኝ አለችው ወረቴን በሙሉ መአበል ወሰደው አላት፤ ታዲያ ለእዚህ ታዝናለህ ያንተም የኔም ዘመዶች ወዳጆች ብዙ ናቸው ተበድረን ትነግዳለህ አለችው፤ እርሱም በአሽሙር ልክ ነሽ ያንቺ ወዳጆች ብዙ ናቸው እኔ ግን ወዳጅ የለኝም ደግሞ በሰጠሁበት አገር ተበድሬ በመጸወትኩበት አገር ለምኜ አልኖርም ወደ ሌላ አገር እሄዳለሁ አላት እኔም ካንተ አልለይም ብላ ተከተለችው በመርከብ ተሳፍረው ሄዱ ከባህሩ መሐከል ሲደርሱእሌኒ ሳምንሽ ካድሺኝ ስወድሽ ጠላሺኝብሎ ሐብሉን አውጥቶ አሳያት እኔ አልሰጠሁትም ህያው እግዚያብሔር ምስክሬ ነው አለችው አላመናት ንጹሕ ከሆንሽ ፈጣሪ ያድንሽ ብሎ በሳጥን አድርጎ ከባህር ጣላት ሳጥኑ በቅዱስ ሚካኤል ጣባቂነት እየተንሳፈፈ ባህር ዳርቻ ደረሰ ቆንስጣ የሚባል ንጉስ አገኛት እጅግ መልከመልካም ነበረችና በክብር አገባት ቆስጠንጢኖስንም ወለደችው ቆንስጣ ሲሞት ልጇ ቆስጠንጢኖስ ነገሰ የጌታን መስቀል ለመፈለግ እየሩሳሌም ወረደች መስቀሉንም አገኘች የዚህ ዜና በሰፊው መስከረም 17 የሚተረክ ነው። 80 ዓመቷ ጌታችን ተገለጸላት ወዳጄ እሌኒ ቅድስት ወደኔ ልወስድሽ ነው ይላታል ደነገጠች ምነው መኖር ትፈልጊያለሽን ይላታል እንተን እንዳመሰግን ብዬ ነው ትለዋለች ስንት ዓመት ልጨምርልሽ ይላታል ይህማ ባንተ ቸርነት መግባት ይሆንብኝ የለምን ትለዋለች እንግዲያውስ 40 ዓመት ጨምሬልሻለሁ አላት 120 ዓመቷ ግንቦት 9 በዛሬዋ ቀን አርፋለች ይህች ቅድስት እናት ያገኘችው ግማደ መስቀል ኢትዮጵያ ውስጥ ይገኛል ለእግዚያብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ከእሌኒ ቅድስት በረከት ያሳትፈን።

ግንቦት 7



በዚህች ቀን ታላቁ የቤተክርስቲያን ሊቅ አቡነ አትናቴዎስ አረፈ። ወላጆቹ አረማውያን ነበሩ ያላመኑ ያልተጠመቁ የአባቱ ስም ሐኪም የእናቱ ስም ማርያም ይባላል መስከረም 20 ቀን ነው የተወለደው። አትናቲዎስ ህጻን እያለ የሰፈሩ ልጆች ደስ የሚል ጨዋታ ሲጫወቱ ይመለከታል ለመሆኑ እንዴት ያለ ጨዋታ ነበር ካሉ እንደ ዘመናችን ህጻናት ሌባና ፖሊስ፤ ...ባሮሽ፤ ኳስ፤ ወይንም እርግጫአልነበረም፤ ስርዓተ ቤተክርስቲያን እየሰሩ ነበር የሚጫወቱት፤ እትናቴዎስ እኔንም ከጫወታችሁ አስገቡኝ አላቸው እነሱም አንተ ያልተጠመቅህ አረማዊ ነህ ከጫወታችን አትገባም አሉት እሺ አጥምቁኝና አስገቡኝ ሲላቸው የጫወታ ጥምቀት አጠመቁት የጫወታ ሊቀ ጳጳስ አድርገው ሾሙትና ወንበር ላይ አስቀመጡት ሰገዱለት በዚያን ወራት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ የነበረው እለእስክንድሮስ ነው ደቀመዛሙርቱን አስከትሎ መንገድ ሲሄድ የእነዚህ ህጻናትን ጫወታ በመገረም ቆሞ ተመለከተ፤አባታችን ከነዚህ ህጻናት ምን ቁም ነገር ይገኛል ብለህ ትመለከታቸዋልህ አሉት፤እርሱም ይገኛል እንጂ ልጆቼ እነዚህ ህጻናት ያደረጉት በኃለኛው ዘመን እግዚያብሔር በእኔ ላይ አድሮ የሚሰራው ስርዓት ነው፤እነሆ በግብጽ ምድር ጽኑ ርሀብ ይከሰታል የዚህ ህጻን አባቱ ይሞታል እናቱም እንዳሳድገው አምጥታ ለእኔ ትሰጠኛለች ከእኔ በኃላ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ የሚሆነው ይህ ህጻን ነው ብሎ ትንቢት ተናገረለት፤ እንዳለውም ሆነ አባቱ ሲሞት እናቱ ቢኖርም ቢሞትም ከዚህ በኃላ አባቱ አንተ ነህ ብላ አደራ ሰጠችው፤እርሱም በመልካም ስነ ምግባር አሳደገው ዲቁና ቅስና ሾመው በኃላም እርሱ ሲሞት 20ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ እድርገው ሾመውታል፤ በዚህ በሹመቱ ወራት ብዙ ድርሳናትን ተግሳጻትን መልዕክታትን ጽፏል፤ ግሩም ቅዳሴም ደርሷል፤ እንዲያውም በዛሬዋ ቀን አብዛኞቹ አብያተክርስቲያናት ቅዳሴ እትናቴዎስን ነው የሚቀደሰው፤ እንዴት ያለ ግሩም ቅዳሴ ነው/// በነገራችን ላይ አቡነ አትናቴዎስ የመጀመሪያውን የኢትዮጰያን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃንን ቀብቶ የሾመ አባት ነው፤ይህ ታሪክ ደግሞ በሁለተኛ ደረጃና በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ደረጃ የታሪክ ትምህርት ካሪኩለም ውስጥ የተካተተ ነው። አቡነ አትናቴዎስ 318 ሊቃውን በኒቂያ ጉባዬ አርዮስን ተከራክረው ሲረቱ አፈጉባዬ የነበረ አባት ነው፤ ልክ እንደ ዲዮስቆሮስ በደሴተ ጋግራን ለሰባት ዓመት በግዞት ኖሯል፤ይህን አባት የማይጠቅሰው ሊቅ የለም፤ ሃይማኖተ አበው ላይ በስፋት ይገኛል፤ ሊቀ ጳጳስ ሆኖ 46 ዓመት ህዝቡን በፍቅር ካገለገለ በኃላ ግንቦት 7 ቀን በክብር አርፏል፤ በረከቱ ይደርብን