Showing posts with label ውዳሴ ማርያም. Show all posts
Showing posts with label ውዳሴ ማርያም. Show all posts

Wednesday, November 14, 2012

ህዳር 6

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ህዳር 6 በዚህች ቀን እመቤታችን ከልጇ ጋር 3 ዓመት ከ 6 ወር በስደት ከተንገላታች በኃላ ወደ አገራቸው የተመለሱበት ቀን ነው፤ ከግብጽ ሲመለሱ ጌታችን በእመቤታችን ጀረባ ላይ ሆኖ እነዚያ እውራንን ባበሩ ጣቶቹ ወደ ኢትዮጵያ ይጠቁም ያመለክት ነበር፤ እመቤታችንም ልጄ ሆይ ለምንድነው ጣትህን የምታመለክተው ብተለው "ያቺ የተባረከች አገር ናት እኔን የሚያመልኩ አንቺን የሚማልዱ በፍቅርሽ የነደዱ ቅዱሳን መነኮሳት የሚፈልቁባት አገር፤ ያንቺ ዘመዶች ሰቅለው ይገድሉኛ በዚህች አገር ያሉ ግን ሳይዩኝ ያመኑኛል፤ አስራት በኩራትሽ ትሁን ብሎ ሰጥቷታል፡፡ በኪደተ እግራቸውም ጣና ሐይቅን፤ ዋልድባንና ሌሎችንም ቦታዎች ዞረው እንደባረኩ ድርሳነ ኡራኤልና ተአምረ ማርያም ላይ በስፋት ተጽፏል፡፡ እምቤታችንን ከሐና መህጸን ፈጥሮ ከፍጥረተ ዓለም ለይቶ ከሁሉ አልቆ የእናት አማላጅ ትሁናችሁ ብሎ የሰጠን እግዚያብሔር ይመስገን። ዳግመኛም በዛሬዋ ቀን በኢትዮጰያ ምድር ታላቅ አምድ ወደቀ ይህም የመናገሻው ባህታዊ አባ ኤልያስ ነው፤ በ 400 ዓመት እድሜው ህዳር 6 1874 ዓ/ም አረፈ፤ በአጼ ምኒሊክ ዘመነ መንግስት ማለት ነው፤ የቅርብ ጊዜ ነው፤ ይህ አባት

Tuesday, November 13, 2012

ህዳር 3



 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ህዳር

በዚህች ቀን ጻድቁ ንጉስ ነአኩቶ ለአብ አረፈ፤ ይህ ጻድቅ የቅዱስ ላሊበላ የወንድም ልጅ ነው አባቱ ሐርበይ እናቱ መርኬዛ ይባላሉ፤ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ ክህነትን ከንግስና ይዘው ኢትዮጰያን ከመሩ አራቱ የዛጌ ነገስታት አንዱ ነው፤ ቤተክርስቲያን ለነዚህ አራት ነገስታት ጽላት ቀርጻላቸው ቤተክርስቲያን አንጻላቸው የቅድስና ስም ሰጥታቸው ታከብራቸዋለች፤ ይምርሃነ ክርስቶስ፤ላሊበላ ነአኩቶ ለአብና ገብረ ማርያም ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ በነገሰበት 40 ዓመት ሙሉ አርብ አርብ ቀን የጌታን ህማም እያሰበ በዘውዱ ፋንታ የእሾህ አክሊል ደፍቶ፤5 ጦር ዙሪያውን ተክሎ እየደማ እያለቀሰ ሲጸልይ ሲሰግድ ይውል ነበር፤ከእለታት በአንዱ ቀን ጌታችን ተገለጸለት እንዲህም አለው ወዳጄ ነአኩቶ ለአብ እኔ ለዓለም ደሜን ያፈሰስኩት አንድ ቀን ነው፤ አንተ ግን 40 ዓመት ሙሉ ደምህንንና እንባህን ስታፈስ ኖርክ ይበቃሃል አሁን ወደ እኔ ልወስድህ ነው ይለዋል፤ነአኩቶ ለአብም ጌታችንንጌታዬ ሆይ እዚህ ቦታ እኔን ብለው የሚመጡ ወገኖቼን ማርልኝ ይለዋልጌታም እውነት እልሃለው ቦታህን ባይረግጥ ዝክርህን ባያዘክር እንኳን ዝናህን ሰምቶ ያሰበህን ኃጢያቱ ምን ቢበዛ እምርልሃለው፤ ዳግመኛም እልሃለው 40 ዓመት ሙሉ እንባህን ያፈሰስክባት ይህች ድንጋይ እስከ እለተ ምጽአት እያነባች ትኖራለች ከዚህ ለሚጠጡ ለሚጠመቁ ድህነት ይሁናቸው ብሎታል፤ ዛሬም ድረስ የነአኩቶ ለአብ ቤተክርስቲያኑ ባለበት ከጣራው ስር ጻበሉ እየቆየ ጠብ ጠብ ይላል፤ክረምት ከበጋ እይለይም እንዲያውም በበጋ መጠኑ ይጨምራል ይህ ጸበል እጅግ መድሐኒት ነው፡፡ ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ አሸተን ማርያምን አንጾ ከጨረሰ በኃላ ማዕጠንት ይዞ ቤተክርስቲያኑን ሲያጥን ብዙ ቅዱሳን እጣኑን አሽትተው ቤተክርስቲያን ውስጥ ጥቅጥቅ ብለው ቆሙ፤ እናንተ ደግሞ እንዴት መጣችሁ አላቸው እነርሱም እጣኑን አሽትተን መጣን አሉት በዚህም የተነሳአሸተን ማርያምተብላለች፤ቅዱስ ነአኩቶ ለአብ 70 ዓመቱ ህዳር 3 ቀን እንደነ ሄኖክ ተሰውሯል። በረከቱ ይደርብን፡፡  

ምንጭ የይምርሃነ ክርስቶስና የነአኩቶ ለአብ ገድል


Wednesday, November 7, 2012

መስከረም 2



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
 
መስከረም 2



በዚህች ቀን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አንገቱ የተቆረጠበት ቀን ነው። የ 2 ዓመት ከመንፈቅ ህጻን እያለ ከእናቱ ኤልሳቤጥ ጋር ወደ ሲና በርሃ ተሰደደ፤ በ 7 ዓመቱ እናቱ በርሃ ላይ ሞተችበት በድኗን ታቅፎ አለቀሰ፤ በዚህ ወቅት ጌታችን ህጻን ነበር ለእመቤታችን ዘመድሽ ኤልሳቤጥ አርፋለችና ወደዚያው እንሂድ አላት ዮሴፍና ሶሎሜን ጨምረው ወደ ዮሐንስ መጡ ብቻውንም ሲያለቅስ አገኙት፤ ኤልሳቤጥን ገንዘው ቀበሯት፤ እመቤታችን ለጌታ ዮሐንስን ይዘነው እንሂድ አለችው፤ ጌታም የለም መንገዴን ጠራጊ ነውና እዚሁ በረሃ ነው የሚያድገው አላት። ቅዱስ ዮሐንስ ኤልሳቤጥ ያሰፋችለት የግመል ቆዳ ነበረች እርሷን ለብሶ አንቦጣ የሚባል ቅጠልና የበርሃ ማር እየበላ በብህትውና ኖረ።30 ዓመት ከመንፈቅ ሲሆነው ወደ ዮርዳኖስ ወጣ የጌታን መንገድ አቅኑ እያለ አዋጅ ተናገረ ጌታንም አጠመቀ፤ ጳጉሜ 1 ሄሮድስ እስርቤት ከተተው በዛሬዋ ቀንም አንገቱን ቆረጠው፤ የተቆረጠች አንገቱ ክንፍ አውጥታ 15 ዓመት በደቡብ አረቢያና አካባቢው ሰብካ ሚያዚያ 15 ቀን በክብር አረፈ፤ ደቀመዛሙርቱ ከቀሪው አካሉ ጋር አድርገው ቀበሩት። በረከቱ ይደርብን




ይህን ቢቡት